XtGem Forum catalog
free book gift

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።


Iqra

=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=

ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ


1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።

2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።

3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።

4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
Iqra
Iqra

Homeየወጣቱ ተልዕኮ ምንነትየአቂዳ ትምህርቶችየሶላት መመሪያረመዷንሙስሊም ሴቶችኢስላማዊ ቤተሰብከታሪክ ማህደርሐዲስለወጣቶችትምህርትና መሰረታዊ ክህሎታችጤናችንግጥምጥያቄና መልስኢስላማዊ መዝገበ ቃላት
free book gift

=<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=

ያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም አንብብ!

free book gift

በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው።

free book gift

.:☀:.♥ማን እንደ እናት!!!♥.:☀:.


I love you mam

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ርህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

-<{አል-ቁርአን 46 : 15})>-

«ሰውንም ለወላጆቹ በጐ መዋልን በጥብቅ አዘዝነው። እናቱ በችግር ላይ ሆና አረገዘችው፤ በችግርም ላይ ሆና ወለደችው፤....»

-<({አል-ቁርአን 17:23-24})>-

(23) ጌታችሁም ከእሱ በቀር ያለን ነገር እንዳታመልኩ እና ለቤተሰቦቻችሁ ቅን ትሆኑ ዘንድ ደነገገ። በአንተ ዘንድ ኾነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው የእርጅና እድሜ በደረሱ ጊዜ <ኡፉ> አትበላቸው ፤ አትገላምጣቸውም። መልካምን ቃል ተናገራቸው።

(24) በእዝነት የውርደትና የሽንፈት ክንፍህን ዝቅ አድርግላቸው። እናም «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ ሁሉ ምህረትህን ስጣቸው» በል።

-<({አል-ቁርአን 29 : 8})>-

«የሰው ልጅ ለወላጆቹ መልካምና ታዛዥ ይሆን ዘንድ አዘዝነው። ነገርግን እውቀት በሌለህ ነገር በኔ ላይ እንድታሻርክ ቢጥሩ(ቢያስገድዱህ) አትታዘዛቸው፤...»


.♥. ሐዲስ .♥.


۵ በአህመድና በአነሳእይ እንደተዘገበው
ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ): ጀነት ከናታችሁ እግር ስር ናት ብለዋል።

ቡሐሪ መጽሐፍ 73, ጥራዝ 8, የሐ.ቁጥር 2

۵ አቡሑረይራ(ረ.ዐ) እንደተረከው
አንድ ሰው ወደ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) መጣና ያረሱ ሉሏህ! በጣም ላገለግለው የሚገባ ማነው? ሲል ጠየቀ። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናትህ አሉት። ሰውየው ቀጣዩስ ማነው? ሲል ጠየቀ። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እናትህ አሉት። ቀጣዩስ ማነው? ሲል በድጋሚ ጠየቀ። ረሱልም(ሰ.ዐ.ወ) እናትህ አሉት። ለአራተኛ ጊዜ ቀጣዩስ ማነው? ሲል ጠየቃቸው። ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) አባትህ አሉት።

۵ በአቡ ዳውድና በኢብን ማጃ እንደተዘገበው
አቡ ኡሰይድ እንዳወራው
አንዴ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) ጋር ቁጭ ብለን ከሰላማህ ጐሳ የሆነ አንድ ሰው መጣና እንዲህ አላቸው:- የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! ወላጆቼ ከሞቱ ብኻላ በኔ ላይ ሃቅ አላቸውን? ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ አሉ:- አዎ! አሏህ በምህረቱና በእዝነቱ ይባርካቸው ዘንድ ዱአ ልታደርግላቸው ይገባል! ለሰዎች የገቡትን ቃልቂዳን አሟላ፤ ጓደኞቻቸውንና ዝምድናቸውን አክብር ብለዋል።


.♥.♥ማን እንደ እናት!!!♥.♥.


.♥.♥ማን እንደ እናት!!!♥.♥.

እናት የዛሬ ማንነታችን ስትሆን በመልካም ስብዕና ኮትኩታ ፣ ከመጥፎ ነገር ከልክላ አሳድጋናለች። የወደፊት ግባችን ምን መሆን እንዳለበት ሁሌም ትጨነቃለች ፣ ታልማለች። እሷ ሳትበላ እኛን ታጐርሳለች፤ የራሷን ስሜት ገድባ የኛን ታሟላለች። ስናለቅስ ልቧ በፍርሃት ፣ በጭንቀትና በትካዜ ይዋጣል። እሩቅ ቦታ ስንሄድ ሃሳቧ ሁሉ ጥቅልል ብሎ ስለኛ ደህነነት ማሰብና መጨነቅ ይሆናል። በምን ሁኔታ ላይ እንደሆን ዘወትር ትጠበባለች።

ታዲያ እናትን መገላመጥ መሳደብ በሷ ላይ መፎከስ ቀርቶ ኡፍ እንኴ ፈፅሞ ልንላት አይገባም። አይደለም እንዴ?

ይህን ሁሉ ፍቅር እዝነት ሰታን ልቧን መስበር ትልቅ ወንጀል ነው። እናም ውድ ሙስሊም እህት ወንድሞቼ እናታችነን በቅን መንፈስ እናገልግላት፤ እንከባከባት። የእናቱን ደስታ ፣ ፈገግታ ማየት የማይሻ ማን ይኖር ይሆን?

አሏህ በትንሹም ቢሆን የናታቸውን ሃቅ ከሚወጡት መካከል ያድርገን!!!


Ï
:¨·.·¨:
`·.. U Mam with heart and soul


Websites:
http://youth-mission.mobie.in

http://youth-mission.blogspot.com

fb page:
http://facebook.com/youth.mission29

© ዝግጅት በአህመድ የሱፍ
2006

1338

የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
free book gift

Download Islamic Books
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ

Important Web Links


free book gift

free book gift

free book gift

ስለወጣቱ ተልዕኮ ምንነት ለማወቅ እዚህ ላይ ክሊክ ያድርጉ

Copyright©Youth-Mission የወጣቱ ተልዕኮ